Yezinna Negash – Seqota Lyrics

አኸ አኸ ዘመዴ ነይ ነይ ያገሬ ልጅ
እስኪ ወዲያ ሄደሽ ወዲህ ተመለሺ
ለኛም ደስ ይበለን ሰዎቹም ይዩሺ
አላማጣ ውዬ መልሼ አላማጣ
በበሽታዬ ላይ በሽታ አላመጣ
ባንቻሮበ ገዳም በሶስቱ መንደር
እኔ የሽማግሌ ልጅ ተብዬ ነበር
ይኸው ባንተ በኩል ስሜ ሲሰበር
አንተ የምናምን ልጅ እኔን ሰው ያወቀኝ
እንዳልመጣ ኮራው እንዳልቀር ጨነቀኝ
እኮ
ሰብ ሰብ
እም አለምዬ
አኸ ኸ ዘመዴ
አንቺም ሰው ሆንሽና ሰው ቀጥሮ መጥፋት
እርሶም ሰው ሁነው ሰው ቀጥሮ መጥፋት
ደማደሞ ከንፈር አንቺ ዶዘር ፊት
ናናናና ናናአለምዬ
አልቻሜ ወልቻሜ የኔ ጥምር እግር
አንተ አለኸኝ ብዬ ለሰውም አልነግር
ሰብሰብ
አለም አለምዬ
አኸ ኸ ዘመዴ
እንካን አንቺንና ጥንብቻ ሆዷን
እንካን አንቺንና ጎተራ ሆዷን
ጥለናት መተናል የወይን ሀረጓን
እነይነይነይ
እም አለምዬ
አንተን ማን አረገህ የብርሌ ጠጅ
ግዜ ማሳለፊያ ቅራሬ ነህ እንጂ
ያንተ ያለህ ሰፕ
እም አለምዬ
አኸ ኸ ዘመዴ
ከንግዲስ ወዲያ አልለማመጥም
ጥርግ በል
ከንግዲስ ወዲያ አልለማመንም
እኔም አልፈልግም
እንደናዝሬት በርሜል ያንከባልሽ ማንም

Comments (0)